የሀገር ውስጥ ዜና

ተጨማሪ 656 ሰዎች ኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው የስምንት ሰዎች ህይወት አልፏል

By Tibebu Kebede

February 08, 2021

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 1 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፊት 24 ሰአታት ለ5 ሺህ 147 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 656 ሰዎች ኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ፡፡

ከዚህ ባለፈም ባለፉት 24 ሰአታት ውስጥ 137 ሰዎች ከቫይረሱ ሲያገግሙ በአጠቃላይም 125 ሺህ 756 ሰዎች አገግመዋል፡፡

እንዲሁም የስምንት ሰዎች ህይወት ማለፉን ተከትሎም 2 ሺህ 156 ሰዎች በቫይረሱ ሳቢያ ለህልፈት ተዳርገዋል፡፡

225 ሰዎች ደግሞ አሁን ላይ በጽኑ ህክምና ላይ ይገኛሉም ነው የተባለው፡፡

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!