የሀገር ውስጥ ዜና

አምባሳደር መለስ ከደቡብ ሱዳንና ጅቡቲ አቻዎቻቸው ጋር ተወያዩ

By Tibebu Kebede

February 15, 2021

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 8 ፡ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በኬንያ የኢፌዴሪ ባለሙሉሥልጣን አምባሳደር መለስ ዓለም ከደቡብ ሱዳን አምባሳደር ቾል ማውት እና የጅቡቲ አምባሳደር ያሲን ኤልሚ ጋር ተወያይተዋል፡፡

አምባሳደር መለስ ዓለም በትግራይ ክልል እየተካሄደ ባለው የሰብዓዊ ድጋፍ እና የመልሶ ግንባታ፣ ከሱዳን ጋር ባለው የድንበር ሁኔታ እንዲሁም በታላቁ ህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር ዙሪያ ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

የጅቡቲና የደቡብ ሱዳን አምባሳደሮች በበኩላቸው የኢትዮጵያ ሠላምና ፀጥታ የሀገሮቻቸው ደህንነት መሆኑን ጠቅሰው በሁሉም መስክ ከኢትዮጵያ ጎን እንደሚቆሙ ገልፀዋል፡፡

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን

የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት መተግበሪያን https://play.google.com/store/apps/details?id=com.companyname.FanaAm በስልክዎ በመጫን ቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት፣ ኤፍኤም 98.1 እና ብሄራዊ ሬዲዮን ይከታተሉ፡፡ ቪዲዮዎችንም ይመልከቱ፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!