ስፓርት

በቻምፒየንስ ሊጉ ፖርቶ እና ዶርትመንድ ድል ቀንቷቸዋል

By Tibebu Kebede

February 18, 2021

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ትናንት ምሽት ተደርገዋል፡፡

በምሽቱ ጨዋታ ወደ ፖርቹጋል ያቀናው ጁቬንቱስ በፖርቶ 2 ለ 1 ተሸንፏል፡፡

ታሬሚ እና ማሬጋ ለፖርቶ የድል ጎሎቹን ሲያስቆጥሩ ኪዬዛ ጁቬንቱስ ለመልሱ ጨዋታ ተስፋ የሰነቀባትን ማስተዛዘኛ ጎል አስቆጥሯል፡፡

በሌላኛው የምሽቱ ጨዋታ ደግሞ በሜዳው ቦሩሲያ ዶርትመንድን ያስተናገደው ሴቪያ ሽንፈት አስተናግዷል፡፡

ሴቪያ በፈርናንዴዝ ሳኤዝ ጎል ቀዳሚ ቢሆንም ዶርትመንድ በሃላንድ ሁለት ጎሎች እና ዳሁድ 1 ጎል ጨዋታውን 3 ለ 1 መምራት ችሏል፡፡

ደ ዮንግ ለባለሜዳዎቹ በጨዋታው መጠናቀቂያ ከሽንፈት ያልታደገቻቸውን ጎል አስቆጥሮ ጨዋታው 3 ለ 2 ተጠናቋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!