Fana: At a Speed of Life!

የገንዘብ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ ከጀርመን አምባሳደር ጋር የሃገራቱን ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት መንገድ ላይ ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 11 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሺዴ በኢትዮጵያ ከጀርመን አምባሳደር ስቴፈን አውር ጋር ተወያዩ፡፡

በውይይታቸው ወቅት የሁለቱን ሃገራት ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ መክረዋል፡፡

በዚህ ወቅትም ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ከሆኑ ሃገራት መካከል አንደኛዋ መሆኗን ጠቅሰው፥ የጀርመን የንግድ ተቋማት በኢትዮጵያ የሚያደርጉትን የኢንቨስትመንት ተሳትፎ እንዲቀጥሉ አበረታተዋል፡፡

የሃገራቱን የቆየ አጋርነት ያነሱት ሚኒስትሩ ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን ድጋፍም አድንቀዋል፡፡

ሚኒስትሩ በትግራይ ክልል እየተደረገ ስላለው ሰብአዊ ድጋፍና መልሶ ግንባታ ሂደትን በተመለከተም ለአምባሳደሩ ገለጻ አድርገውላቸዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.