የሀገር ውስጥ ዜና

የዓለም ሎሬት ዶ/ር ጥበበ የማነ ብርሃን አረፉ

By Meseret Awoke

February 21, 2021

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 13 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም ሎሬት ዶ/ር ጥበበ የማነ ብርሃን በሕክምና ሙያ፣ በሀገር ሽማግሌነት፣ በዕርዳታ አስተባባሪነት እና በዕርቀ ሰላም ኮሚሽን አባልነት ሀገራቸውን ያገለገሉ ነበሩ ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የዓለም ሎሬት ዶ/ር ጥበበ የማነ ብርሃን በማረፋቸውን የተሰማቸውን ኀዘን ገልጸው ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጆቻቸውና ለኢትዮጵያውያን ሁሉ መጽናናትንም ተመኝተዋል ።

የጤና ሚኒስቴር በበኩሉ በተከበሩ የዓለም ሎሬት ዶ/ር ጥበበ የማነ ብርሃን ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ሀዘን ገልጾ በኮቪድ -19 ህይወታቸው ማለፉን አስታውቋል።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!