አዲስ አበባ ፣ የካቲት 21 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) 125ኛው የኢትዮጵያውያንና የጥቁር ህዝቦች የድል በአል በአድዋ የጀግኖች መታሰቢያ በሆነው የአድዋ ድልድይ በድምቀት ተከበረ ።
125ኛው የአድዋ በአል ድል ቀን በስፖርት ቤተሰቡና በየካ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች ፣ ጥሪ በተደረገላቸው እንግዶች ተከብሯል ።
በወጣው መርሀ ግብር በከተማው የሚገኙ 36 ፌዴሬሽኖች ፣ አሶሴሽኖች ልዩ ልዩ ስፖርታዊ ፌስቲቫል ፣ ትርዒት እንዲሁም የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጨምሮ ተካሂዷል ።
የአድዋ ድልን የሚዘክሩ መልዕክቶችና ሁነቶችም ተስተጋብተዋል ።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!