የሀገር ውስጥ ዜና

125ኛው የአድዋ የድል በአል በአድዋ ድልድይ ተከበረ

By Meseret Awoke

February 28, 2021

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 21 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) 125ኛው የኢትዮጵያውያንና የጥቁር ህዝቦች የድል በአል በአድዋ የጀግኖች መታሰቢያ በሆነው የአድዋ ድልድይ በድምቀት ተከበረ ።

125ኛው የአድዋ በአል ድል ቀን በስፖርት ቤተሰቡና በየካ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች ፣ ጥሪ በተደረገላቸው እንግዶች ተከብሯል ።

በወጣው መርሀ ግብር በከተማው የሚገኙ 36 ፌዴሬሽኖች ፣ አሶሴሽኖች ልዩ ልዩ ስፖርታዊ ፌስቲቫል ፣ ትርዒት እንዲሁም የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጨምሮ ተካሂዷል ።

የአድዋ ድልን የሚዘክሩ መልዕክቶችና ሁነቶችም ተስተጋብተዋል ።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!