ከውጭ ያለውን ጠላታችን ከማሸነፋችን በፊት ከውስጣችን ያለውን ቂም እና ጥላቻ ማስወገድ ይገባል-ጠ/ሚ ዐቢይ
አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በደቡብ አፍሪካ ይፋዊ የስራ ጉብኝት በማድረግ ላይ የሚገኙት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ዛሬ በጆሐንስበርግ ከተማ ኢምፔሪያል ዎንደረርስ ክሪኬት ስታዲየም በመገኘት በሀገሪቱ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን መልዕክት አስተላልፈዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው በደቡብ አፍሪካ በሚኖሩ ኢትዮጵያውን ዜጎች ጉዳይ ዙሪያ ከሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳ ጋር መምከራቸውን ተናግረዋል።