ቢዝነስ

ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌህ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጂቡቲ ቅርንጫፍን መርቀው ከፈቱ

By Tibebu Kebede

January 13, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የጂቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌህ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በጂቡቲ የከፈተውን ቅርንጫፍ በትናንትናው እለት መርቀው ከፍተዋል።

በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌህን ጨምሮ በጂቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር አብዱላዚዝ መሃመድ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ ባጫ ጊና እንዲሁም ሌሎች የባንኩ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።