አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የጂቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌህ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በጂቡቲ የከፈተውን ቅርንጫፍ በትናንትናው እለት መርቀው ከፍተዋል።
በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌህን ጨምሮ በጂቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር አብዱላዚዝ መሃመድ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ ባጫ ጊና እንዲሁም ሌሎች የባንኩ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።