የሀገር ውስጥ ዜና

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከቤቶች ልማት ጋር በተያያዘ 50 ቢሊየን ብር የባንክ እዳ እንዳለበት ተገለፀ

By Tibebu Kebede

January 13, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከቤቶች ልማት ጋር በተያያዘ 50 ቢሊየን ብር የባንክ እዳ እንዳለበት ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ገለጹ።

የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ የተመራ የምክር ቤቱ አባል ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ታከለ ኡማ እና ካቢኔያቸው ጋር ዛሬ ተወያይተዋል።