የሀገር ውስጥ ዜና

ፕሬዚዳንት ሳሕለወርቅ ዘውዴ ‘ሆፕ ፎር ፋዘርለስ’ የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅትን ጎበኙ

By Tibebu Kebede

March 10, 2021

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 1፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ሳሕለወርቅ ዘውዴ ‘ሆፕ ፎር ፋዘርለስ’ የተሰኘ ግብረ ሠናይ ድርጅትን ጎበኙ።

በ2008 ዓ.ም የተቋቋመው ‘ሆፕ ፎር ፋዘርለስ’ የተሰኘው አገር በቀል ግብረ ሰናይ ድርጅት ወላጅ አልባና ድጋፍ የሚሹ ህጻናትን ለመደገፍ የተቋቋመ  መሆኑን ኢዜአ ዘግቧል።

ድርጅቱ በትምህርት መርጃ መሳሪያዎች አቅርቦትና መሰል ተግባራት ላይ የሚሰራ ሲሆን ከአዲስ አበባ ሠራተኛና ማኅበራዊ ቢሮ ጋር በመተባበር የአገር ውስጥ ጉዲፈቻንም ያመቻቻል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!