ለሞዴል አርሶ አደሮች በፊንፊኔ ዙሪያ ኦሮሚያ ልዩ ዞን ለቤት መስሪያ የሚሆን የመሬት ርክክብ ተካሄደ
በመርሀ ግብሩ ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እና ሞዴል አርሶ አደሮች ተገኝተዋል።
በመርሀ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ÷ ከዚህ ቀደም በነበሩት ስርዓቶች አርሶአደሩ በተለያዩ ምክንያቶች አላግባብ መሬቱን ሲነጠቅና ለከፋ ችግር ሲጋለጥ መቆየቱን አንስተዋል።
አሁን ላይ ግን አርሶ አደሮቹ ህጋዊ በሆነ መልኩ ተደራጅተው የቤት መስሪያ ቦታ እንዲሰጣቸው መደረጉን ነው ርዕሰ መስተዳድሩ ያነሱት።
በትዝታ ደሳለኝ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!