የሀገር ውስጥ ዜና

በፒያሳ አካባቢ በ7 የንግድ ሱቆች ላይ የእሳት አደጋ ደረሰ

By Tibebu Kebede

January 15, 2020

አዲስ አበባ ፣ ጥር 6 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ፒያሳ አካባቢ በሚገኙ ሰባት የንግድ ሱቆች ላይ የእሳት አደጋ ደረሰ፡፡

4 ሰዓት ከ40 ደቂቃ ላይ በተከሰተው በዚህ እሳት አደጋ ሰባት ሱቆች ላይ ቃጠሎ የደረሰ ሲሆን፥ ከእነዚህ ውስጥ ሁለት ሱቆች ሙሉ በሙሉ መውደማቸው ተገልጿል።