በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በትንሹ መናኸሪያ የእሳት አደጋ ደረሰ

By Tibebu Kebede

April 04, 2021

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 26 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አውቶቢስተራ አካባቢ በተለምዶ ትንሹ መናኸርያ ተብሎ በሚጠራው የአውቶቡስ መናኸሪያ ላይ የእሳት አደጋ ደርሷል።

ዛሬ ከሰዓት በኋላ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የአጭር ርቀት መስመሮችን የትራንስፖርት አገልገሎት በሚሰጠው በተለምዶ ስሙ ትንሹ መናኸሪያ ላይ እሳት መድረሱን ኢዜአ የአይን እማኞች ጠቅሶ ዘግቧል።

በአሁኑ ወቅትም  የተከሰተውን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር የእሳትና ድንገተኛ አደጋ ሰራተኞች  ርብርብ እያደረጉ እንደሚገኝም ዘገባው አመልክቷል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!