የሀገር ውስጥ ዜና

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ከጀመረ ዛሬ 75ኛ ዓመቱን ያዘ

By Abrham Fekede

April 08, 2021

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 30፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ የጀመረበትን 75ኛ ዓመት በማክበር ላይ ይገኛል፡፡

አየር መንገዱ ከ75 ዓመታት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን ነበር በረራ የጀመረው፡፡

በ1938 ዓ.ም/በፈረንጆቹ 1946 የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ በረራ ከአዲስ አበባ ተነሥቶ በአስመራ በኩል ካይሮ (ግብፅ) አረፈ።

አየር መንገዱ በረራ የጀመረው ከተመሰረት ከአንድ ዓመት ቆይታ በኋላ እንደነበር ይታወሳል፡፡

ዛሬ በዓለማችን ከሚገኙ አንጋፋ አየር መንገዶች አንዱ ለመሆን የበቃው አየር መንገዱ 75ኛ ዓመቱን በማክበር ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል።

አየር መንገዱ ለደንበኞቹና ለሰራተኞቹ ለ75ኛ ዓመቱ እንኳን አደረሳቹ ብሏል።

75 years ago today,in 1946, Ethiopian Airlines operated its 1st scheduled flight with Douglas C-47 Skytrain aircraft from Addis Ababa to Cairo via Asmara.Happy 75th anniversary to our valued customers & all hard working employees who made the airline shine high in the sky. #ET75 pic.twitter.com/WEnvR0ZEPH

— Ethiopian Airlines (@flyethiopian) April 8, 2021

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!