የሀገር ውስጥ ዜና

በማይካድራ በተፈጸመው ወንጀል ተሳትፎ አላቸው በተባሉ ተጠርጣሪዎች ላይ  የተጀመረው ምስክር የመስማት ሂደት ዛሬም ቀጥሏል

By Abrham Fekede

April 14, 2021

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 6፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) በማይካድራ ለበርካታ ንጹሓን ዜጎች ሞት እና ንብረት መውደም ወንጀል ተሳትፎ አላቸው በተባሉ 21 ተጠርጣሪዎች ላይ የተጀመረው ምስክር የመስማት ሂደት ዛሬም ቀጥሏል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ላይ ማስረጃ ለማቆየት አቃቤ ህግ የቅድመ ምርመራ ምስክር ለመስማት መዝገብ መክፈቱ ይታወቃል፡፡

ይህንን ተከትሎም በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍድር ቤት አራዳ ምድብ ችሎት የአቃቤ ህግ ትላንት ካቀረባቸው 11 ምስክሮች ውስጥ ሦስቱን አሰምቷል፡፡

ቀሪዎቹን ደግሞ በዛሬው ዕለት እያሰማ ይገኛል፡፡

በታሪክ አዱኛ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን