የሀገር ውስጥ ዜና

ዶክተር ፋና ሀጎስ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ሆነው ተሾሙ

By Tibebu Kebede

April 15, 2021

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 7 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ዶክተር ፋና ሀጎስ ብርሃኔ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ሆነው ተሾመዋል።

ዶክተር ፋና ሀጎስ ብርሃኔ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በህግ ትምህርት የተቀበሉ ሲሆን ሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪያቸውን በደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ፍሪስቴትና ዋርዊክ ዩኒቨርሲቲ ተምረዋል፡፡

ትምህርታቸውን በመቀጠልም ኬኒያ ናይሮቢ ከሚገኘው የአፍሪካ ሳይንስ አካዳሚ ፖስት ዶክትሬት አግኝተዋል፡፡

በትግራይ ክልል ፍትህ ቢሮ ዐቃቤ ህግ እንዲሁም በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ለ12 አመታት የህግ ትምህርት ክፍል ረዳት ፕሮፌሰር በመሆን አገልግለዋል።

በተጨማሪም የስርዓተ ጾታ ጥናት ኢንስቲቲዩት ዳይሬክተርና የህግና ስነ-መንግስት ኮሌጅ ዲን በመሆን ማገልገላቸውን ኢቢሲ ዘግቧል።

ሹመቱ ከጥቂት ዓመታት በፊት በዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ምንም ተሳትፎ ያልነበራቸውን የሴቶችን ተሳትፎ አንድ እርምጃ የሚያሳድግና ወጣት ኢትዮጵያውያንን የሚያነቃቃ እንደሆነ ይታመናል ተብሏል።

ዶክተር ፋና በአሁኑ ጊዜ የትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት በመሆን እያገለገሉ ነበር።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!