ዓለምአቀፋዊ ዜና

ኮቪድ19 ባላንጣዎቹ ህንድና ፓኪስታንን በጋራ እንዲቆሙ አድርጓቸዋል

By Tibebu Kebede

April 26, 2021

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 18፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ህንድ ለተከታታይ ሶስተኛ ቀን ዓለም ላይ ከፍተኛውን የኮሮና ቫይረስ ተያዦችን ቁጥር አስመዝግባለች።

በቫይረሱ የሚያዙና ህይወታቸው የሚያልፍ ሰዎች ቁጥር ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ መምጣቱ በህንድ የኦክስጅን እና የአልጋ እጥረት እንዲያጋጥም አድርጓል።

ይህን ተከትሎም በርካታ ሀገራት ከህንድ ህዝብ እና መንግስት ጎን መሆናቸውን በመግለፅ ሰው ሰራሽ መተንፈሻን ጨምሮ የተለያዩ ድጋፎችን ለማድረግ እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ።

ፓኪስታናውያን ከህንድ ህዝብና መንግስት ጎን መቆማቸውን ለማሳየት ያሳዩት የትዊተር ዘመቻ የተለየ ሆኗል።

Humanity has no religion! To all my beautiful Indian people, we’re with you in these testing times! #PakistanstandswithIndia

— Dananeer Mobeen 🌻 (@DananeerM) April 24, 2021

በካሽሚር ግዛት የይገባኛል ጥያቄ ምክንያት ሁለቱ ሀገራት በተደጋጋሚ ጦር ተማዘው የነበረ ሲሆን አሁንም በጠላትነት የሚተያዩ ጎረቤት ሀገራት ናቸው።

ሆኖም ፖኪስታናውያን ከህንድ ጋር ከባድ ልዩነት ቢኖራቸውም ከህንድ ጋር እቆማለሁ በሚል መሪ ቃል የትዊተር ዘመቻ ማድረጋቸውን አልጀዚራ ዘግቧል።

የፓኪስታኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ኢምራን ካህን በትዊተር ገፃቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ ከህንድ ጋር መቆማቸውን በመግለፅ በኮቪድ19 ህመም ላይ የሚገኙት በፍጥነት እንዲያገግሙ መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።

I want to express our solidarity with the people of India as they battle a dangerous wave of COVID-19. Our prayers for a speedy recovery go to all those suffering from the pandemic in our neighbourhood & the world. We must fight this global challenge confronting humanity together

— Imran Khan (@ImranKhanPTI) April 24, 2021

በዚህ የፓኪስታናውያን የትዊተር ዘመቻ ታዋቂ ሰዎች ፣ ማህበራዊ አንቂዎች ፣ የመንግስት ባለስልጣናት እና በመላው ፓኪስታን የሚገኙ ዜጎች ለህንዳውያን የአጋርነት መልዕክት አስተላልፈዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!