የሀገር ውስጥ ዜና

የመገናኛ ብዙሃንና የጋዜጠኞች የምርጫ አዘጋገብ የስነምግባርና አሰራር ረቂቅ መመሪያ ውይይት እየተደረገበት ነው

By Tibebu Kebede

January 18, 2020

አዲስ አበባ ፣ ጥር 9፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ለምርጫው ማስፈፀሚያ ባዘጋጃቸው መመሪያዎች ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር መክሯል፡፡

የመገናኛ ብዙሃን እና የጋዜጠኞች የምርጫ አዘጋገብ የስነምግባር እና አሰራር ረቂቅ መመሪያ እና የስነዜጋ እና የመራጮች ትምህርት ፈቃድ አሰጣጥ እና ስነምግባር ረቂቅ መመሪያ ናቸው ውይይት የተካሄደባቸው።