FILE PHOTO: An Ebola survivor who works as a nurse, gets dressed in a protective suit as he prepares to start his shift at an Ebola treatment centre (ETC) in Katwa, near Butembo, in the Democratic Republic of Congo, October 2, 2019. REUTERS/Zohra Bensemra/File Photo

ዓለምአቀፋዊ ዜና

ኮንጎ የኢቦላ ወረርሽኝ በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታወቀች

By Meseret Awoke

May 04, 2021

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 26፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የኢቦላ ወረርሽኝ በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታውቃለች፡፡

በሃገሪቱ ከፈረንጆቹ 2018 እስከ 2020 ድረስ ከ2 ሺህ 200 በላይ ሰዎች በኢቦላ ሳቢያ ለህልፈት ተዳርገዋል፡፡

ወረርሽኙ በቫይረሱ ከተያዙ እና በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መንገድ ግንኙነት የነበራቸውን ከ1 ሺህ 600 የሚበልጡ ሰዎች በማሰስ መርክ የተባለውን የኢቦላ ክትባት እንዲወስዱ መደረጉን የዓለም አቀፉ ድንበር የለሽ የሃኪሞች ቡድን ገልጿል፡፡

የቫይረሱ ምልክት የማይታይበትና ከበሽታው ባገገመ ህመምተኛ የሰውነት ፈሳሾች ውስጥ ቫይረሱ ሊቆይ እንደሚችል ተጠቁሟል፡፡

ቫይረሱ ከ2013 እስከ 2016 ባሉት ዓመታት በምዕራብ አፍሪካ ወደ 11ሺህ ሰዎች ህልፈት መሆኑ ይነገራል፡፡

በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከኮሮና ቫይረስ በተጨማሪ የኢቦላ ዳግም መከሰት ስጋት ፈጥሮ እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡

ምንጭ፡- አልጀዚራ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!