አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 27፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) – ዶክተር አብራሃም በላይ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳድር ዋና ስራ አስፈፃሚ ሆነው ተሾሙ።
የትግራይ ብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንትም የሆኑት ዶ/ር አብራሃም የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ሆነው እየሰሩ ይገኛሉ።
ዶ∕ር አብርሃም በተለያዩ የመንግስት ሃላፊነቶች ላይም አገልግለዋል::
በሃላፊነት ካገለገሉባቸው ተቋማት ውስጥ የኢትዮጵያ ኮሚኒኬሽን ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ መብራት ኃይል ፣ ኢትዮ ኢንጅነሪንግ ግሩፕ የድሮ ሜቴክ ፣ ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ፣ የአምቦ ዩንቨርስቲን በቦርድ ሰብሳቢነት ፤ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቦርድ አባል በመሆን እየሰሩ ይገኛሉ።
በተጨማሪም የህዳሴውን ግድብ ከውድቀት በማዳን ውሰጥ ቁልፍ ሚና እንደተጫወቱ የነገርላቸዋል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!