አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 4 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) 1 ሺህ 442ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በሚከበርበት እለት ለበዓሉ ድምቀት ከማለዳው 12:00 ሰዓት ላይ ዘጠኝ ጊዜ መድፍ እንደሚተኮስ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
በዓሉ በሚከበርበት ግንቦት 5 ቀን 2013 ዓ.ም ለበዓሉ ድምቀት ከማለዳው 12:00 ሰዓት ላይ መድፍ እንደሚተኮስና ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በዓሉ የሰላም የደስታ እንዲሆን መልካም ምኞቱን ገልጿል፡፡
1 ሺህ 442ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል ነገ በመላው ዓለም ይከበራል ፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!