Fana: At a Speed of Life!

በኦሮሚያ ክልል በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች እውቅና እና ሽልማት ተሰጠ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 4 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል በ2012 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች እውቅና እና ሽልማት ተሰጠ፡፡

እውቅናና ሽልማቱ የተሰጠው በ2012 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከ600 በላይ ውጤት ላስመዘገቡ 152 ተማሪዎች ነው፡፡

በእውቅናና ሽልማት መርሐ ግበሩ ላይ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ የኦሮሚያ ብልፅግና ጽህፈት ቤጽ ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ እና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ቶላ በሪሶን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች መገኘታቸውን ኢቢሲ ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.