Fana: At a Speed of Life!

ዶ/ር አብርሃም በላይ አሸጎዳ የሚገኘውን የትራክተሮች መገጣጠሚያ ጎበኙ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 6 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር አብርሃም በላይ አሸጎዳ በሚገኘው የትራክተሮች መገጣጠሚያ ጉብኝት አካሄዱ።

በጉብኝቱ ወቅትም፥ የክልሉ የግብርና ስራ ወደ ነበረበት ለመመለስ በሚደረገው ጥረት በቴክኖሎጂ የታገዘ እርሻ ለማካሄድ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ እንዳለ ገልፀዋል።

ይህን ለማድረግ የሚያግዝና ለግብርና ስራዎችን እንደ ግብአት በመሆን የሚያገለግል የትራክተሮች ከመጎብኘት በተጨማሪ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት እንደተወያዩ ተጠቅሷል።

የትግራይ ክልል አስተዳደር ቅድሚያ ሰጥቶ ከሚሰራቸው እና የሁሉም አካላት የላቀ ትኩረት ከሚሹ ተግባራት አንዱ ግብርና መሆኑን በውይይቱ ተገልጿል ሲል የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘግቧል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.