Fana: At a Speed of Life!

በጎንደር የጥምቀት በዓል ላይ ለታዳሚዎች የተዘጋጀ ርብራብ ተደርምሶ ከ100 በላይ ሰዎች ቀላልና ከባድ ጉዳት ደረሰባቸው

አዲስ አበባ ፣ ጥር 11 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በጎንደር የጥምቀት በዓልን ለመታደም ለመጡ እንግዶች የተዘጋጀ ርብራብ ተደርምሶ ከ100 በላይ ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት መድረሱን የጎንደር ከተማ አስተዳደር የሠላምና ሕዝብ ደኅንነት መምሪያ ገለጸ።

አደጋው ለመቀመጫነት የተሠራው ርብራብ እንጨት ድንገት በመንሸራተቱ መድረሱን የከተማ አስተዳደሩ ሠላምና ደኅንነት መምሪያ ኃላፊ ተስፋ መኮንን ተናግረዋል።

በአደጋው ሳቢያም በርብራብ እንጨቱ ላይ ተቀምጠው የነበሩ ከ100 በላይ ሰዎች ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል ነው ያሉት።

ከዚህ ባለፈም በአደጋው ሳቢያ ለህልፈት የተዳረጉ ሰዎች መኖራቸውንም ገልጸዋል።

በአደጋው ከተጎዱት መካከል የተወሰኑት ሕክምና ተደርጎላቸው ወደ ቤታቸው መመለሳቸውን ጠቅሰው፥ ቀሪዎቹ ሕክምና እየተደረገላቸው እንደሚገኝም አስረድተዋል።

ከታካሚዎቹ መካከል አምስቱ ከባድ ጉዳት ያጋጠማቸው ሲሆን፥ ቀላል ጉዳት ከደረሰባቸው መካከል ሁለት የውጭ ሀገር ዜጎችና ሁለት የፀጥታ ኃይሎች ይገኙበታል ብለዋል።

ለታዳሚዎች የተሰራው እንጨት ከአቅሙ በላይ ሰው መያዙ ለአደጋው መንስኤ ነው ማለታቸውን ከአማራ መገናኛ ብዙሃን ድርጅት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ከተፈጠረው አደጋ ውጭ ምንም ዓይነት የፀጥታ ችግር እንዳልነበረና ታቦታቱ በሠላም ወደ አድባራቱ መግባታቸውን ጠቅሰዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.