የሀገር ውስጥ ዜና

የደቡብ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በመደበኛ ስብሰባው በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመምከር ውሳኔ አሳለፈ

By Tibebu Kebede

January 21, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 12፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የደቡብ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት ባካሄደው 209ኛ መደበኛ ስብሰባው በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመምከር ውሳኔ አሳለፈ።

መስተዳድር ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የማዕድን ስራዎች ረቂቅ ደንብ ላይ በዝርዝር በመወያየት ውሳኔ ማሳለፉን ከክልሉ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።