አዲስ አበባ፣ጥር 12፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲቪክ ማህበራት ለመጪው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ማህበረሰቡን የማንቃት ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ምሁራን አሳሰቡ።
ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት አስተያየታቸውን የሰጡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፓለቲካ ሳይንስ መምህር ዶክተር ደመቀ አጪሶ፥ መጪው ምርጫ ተአማኒ፣ ዴሞክራሲያዊና አሳታፊ በሆነ መልኩ እንዲከናወን የዜጎችን ሰላም ማስከበር ተቀዳሚ ተግባር ሊሆን እንደሚገባ አንስተዋል።