የሀገር ውስጥ ዜና

ተጨማሪ 249 ሰዎች ቫይረሱ ሲገኝባቸው 936 ሰዎች ደግሞ ከቫይረሱ አገግመዋል

By Tibebu Kebede

June 03, 2021

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 26 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰአታት ለ4 ሺህ 376 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 249 ሰዎች ቫይረሱ ተገኘባቸው፡፡

ከዚህ ባለፈም ባለፉት 24 ሰኣት የሰባት ሰዎች በቫይረሱ ሳቢያ ለህልፈት መዳረጋቸውን የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በፌስ ቡክ ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡

በተጨማሪም 367 ሰዎች በጽኑ ህክምና ላይ ሲሆኑ፥ 936 ሰዎች ደግሞ ከቫይረሱ አገግመዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!