የሀገር ውስጥ ዜና

የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት በመዲናው የሚከናወኑ የሪፎርም ስራዎችን ጎበኙ

By Tibebu Kebede

June 04, 2021

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 27 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት አኪንውሚ አዴሲና በአዲስ አበባ ከተማ የሪፎርም ስራዎችን ጎብኝተዋል፡፡

የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ዶክተር አኪንውሚ እና ባልደረቦቻቸው በትናንትናው ዕለት የሪፎርም ስራዎች በመጎብኘታቸው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስሰር ገጻቸው አመስግናዋል፡፡

የባንኩ ፕሬዚዳንት አኪንውሚ አዴሲና በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ለማድረግ ትናንት አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወሳል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!