Fana: At a Speed of Life!

የጃፓኑ ሱምቶም  ከሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ በቴሌኮም ዘርፍ ኢንቨስት እንደሚያደርግ ገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 1፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)የጃፓኑ ሱምቶም  ከሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ በቴሌኮም ዘርፍ ኢንቨስት እንደሚያደርግ ገለጸ።

በቴሌኮም ዘርፍ የውጭ ባለሀብቶች እንዲሳተፉ መንግስት በወሰደው ውሳኔ መሠረት  ጨረታውን ያሸነው  ‘የግሎባል ፓርትነርሽፕ ፎር ኢትዮጵያ ‘ ድርጅት  አንዱ የሆነው የጃፓኑ ሱምቶም÷በቀጣይ አምስት ዓመታት ውስጥ በኢትዮጵያ በቴሌኮም ዘርፍ    ከሁለት ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ  ኢንቨስት ለማድረግ ፍላጎት እንዳለው  የኮርፖሬሽኑ ምክትል ሥራ አስፈጻሚ  አስታወቀ፡፡

የኮርፖሬሽኑ ምክትል ሥራ አስፈጻሚ ቶሽካዙ  ናምቡ የኢንቨስትመንት ዕቅዳቸውን ያስታወቁት በጃፓን የኢትዮጵያ አምባሳደር ካሣ ተክለብርሃን ጋር በተወያዩበት ወቅት ነው፡፡

ምክትል ሥራ አስፈጻሚው ኮርፖሬሽናቸው ከሌሎች አጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን  የኢትዮጵያ መንግስት በግልጸኝነት ባካሄደው  የጨረታ ሂደት  በማሸነፋቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል፡፡

አምባሳደር ከሳ ተክለብረሃን ኮርፖሬሽኑ በጃፓን፣በኤሽያ እና በአፍሪካ ያለው የካበተ ልምድ በአገራችን ኢንቨስት በማድረግ እንዲደግመው ጥሪ ማቅረባቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.