አቶ ደመቀ ከቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

By Tibebu Kebede

June 10, 2021

 

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 3፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይ ጋር በስልክ ተዋያዩ፡፡

በዚህ ወቅትም ሚኒስትሮቹ የየሀገራቱን ሉዓላዊነት ለማክበርና ትብብር ለማስጠቅ ያላቸውን የሁለትዮሽ ፍላጉት መግለፃቸውን አቶ ደመቀ በትዊተር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል፡፡

በተለይ ውስጣዊ ጫናዎችን ያለማንም ጣልቃ ገብነት ለመፍታት በጋራ መቆም በሚችሉበት ሁኔታን በተመለከተ መክረዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!