Fana: At a Speed of Life!

ዜጎች አጠራጣሪ ነገር ሲመለከቱ በ910 የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጡ ጥሪ ቀረበ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 4 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ዜጎች ማንኛውም ለሀገርና ለህዝቦች ሰላምና መረጋጋት እንቅፋት የሚሆኑ እንዲሁም ከሀገራዊ ምርጫው ጋር በተያያዘ የደህንነት ስጋት ሊፈጥሩ የሚችሉ አጠራጣሪ ሁኔታዎችን ሲመለከቱ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አጭር የጥቆማ መስጫ ቁጥር 910ን በመጠቀምና ጥቆማ በመስጠት ለጋራ ደህንነት የበኩላቸውን እንዲወጡ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጥሪ አቀረበ።

የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት የሀገሪቱን ደህንነትና ብሔራዊ ጥቅም የመጠበቅ ተልዕኮ የተሰጠው ተቋም ሲሆን፥ አገልግሎት መስሪያ ቤቱ ተልዕኮውን ለመወጣት የሚያግዙ መረጃዎችን፣ በመሰብሰብና በመተንተን ለሚመለከተውም አካል ይሰጣል።

ተቋሙ ሥራ ቀልጣፋና ውጤታማ እንዲሆን የህብረተሰብ ተሳትፎ ወሳኝ ነው ሲል የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ገልጿል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.