Fana: At a Speed of Life!

ተቋርጦ የነበረው የሶዶ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ህንጻ ግንባታ በአዲስ መልክ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 5 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2004 ዓ.ም ተጀምሮ የተቋረጠው በወላይታ ዞን የሶዶ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ህንጻ ግንባታ ከቀድሞ ህንጻ ተቋራጭ ጋር ያለው ውል ተቋርጦ በአዲስ መልክ ሊጀመር ነው፡፡

የደቡብ ክልል ቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ቢሮ ከኬላ ሀላላ ህንፃ ተቋራጭ ጋር የተቋረጠውን ሥራ ለማስቀጠል በ37 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር የውል ሥምምነት ተፈራርሟል ።

በ2004 ዓ.ም የተጀመረው የሶዶ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ህንፃ በተባለለት ጊዜ ባለማለቁ የተለያዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ሲያስነሳ ቆይቷል።

አዲሱ ተቋራጭ በአንድ አመት ውስጥ አጠናቆ እንዲያስረክብ አደራ እንደተሰጠው የክልሉ ቴክኒክኒክና ሙያ ሥልጠና ቢሮ የልማት ዕቅድ ዳይሬክተሬት ዳይሬክተር አቶ ወልደሰንበት ተናግረዋል፡፡

በኢብራሂም ባዲ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.