የሀገር ውስጥ ዜና

በዳንሻ ከተማ የአሸባሪው ሕወሃትን ግፍ የሚያወግዝ እና የውጭ ጣልቃ ገብነትን የሚቃወም ሰልፍ ተካሄደ

By Meseret Awoke

June 13, 2021

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)በወልቃይት ጠገዴ ዳንሻ ከተማ የአሸባሪውን ሕወሃት ግፍ የሚያወግዝና የውጭ ጣልቃ ገብነትን የሚቃወም ሰልፍ ተካሂዷል።

በአሸባሪው ሕወሃት የሥልጣን ዘመን የደረሰውን ግፍ የሚያወግዙና የውጭ ጣልቃ ገብነትን የሚቃወሙ ሰልፎችም በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራና የተለያዩ ከተሞች ሲደረጉ መቆዬታቸው ይታወሳል።

በሑመራ ከተማ የተጀመረው ሰልፍም ዛሬ በዳንሻ ከተማ የቀጠለ ሲሆን፥ ነዋሪዎቹ የአሸባሪው ህወሃት ቡድን ግፍ እና የውጭ ጣልቃ ገብነትን የሚያወግዝ ሰልፍ በማካሄድ ላይ እንደሚገኙ አሚኮ ዘግቧል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!