ዓለምአቀፋዊ ዜና

የቡድን 7 አባል ሀገራት ተጨማሪ 1 ቢሊየን የኮቪድ ክትባት ለታዳጊ ሃገራት ለመለገስ ተስማሙ

By Tibebu Kebede

June 14, 2021

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 7 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የቡድን 7 አባል ሀገራት ተጨማሪ 1 ቢሊየን የኮቪድ19 ክትባት ለታዳጊ ሀገራት ለመለገስ ተስማሙ።

ለመለገስ የተስማሙት የክትባት መጠን በትናንትናው ዕለት ለመስጠት ከተስማሙት 1 ቢሊየን ክትባት በተጨማሪነት የሚሰጥ መሆኑ ተገልጿል፡፡

አሜሪካ 500 ሺህ የፋይዘር ክትባት የምታቀርብ ሲሆን ክትባቱ ከሚቀጥለው ነሐሴ ወር ጀምሮ ይሰራጫል ተብሏል፡፡

ይህም ለ92 ታዳጊ ሃገራት የሚዳረስ መሆኑን የሲ ጂ ቲ ኤን ዘገባ ያመላክታል፡፡

በተጨማሪነት የሚለገሰውን ክትባት ተከትሎም ቡድኑ ካለፈው የፈረንጆቹ አመት ጀምሮ የሚሰጠውን የክትባት መጠን ወደ 2 ነጥብ 3 ቢሊየን ያደርሰዋል ነው የተባለው፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!