የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያና ፊንላንድ ለኮዋሽ ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ ከ1 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በላይ ስምምነት ተፈራረሙ

By Tibebu Kebede

January 23, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 14 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ እና ፊንላንድ በአምስት ክልሎች ለሚተገበረው የማህበረሰብ ንጹህ መጠጥ ውሃ እና የጤና አጠባበቅ (ኮዋሽ) ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የሚውል የ1 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ስምምነት ተፈራረሙ።

ከፊንላንድ የመጡ የኮዋሽ ፕሮጀክት ሃላፊዎች፣ የቴክኒክ አማካሪዎች፣ የኢትዮጵያ የኮዋሽ አስተባባሪ እና የአማራ ክልል የማህበረሰብ አቀፍ የኮዋሽ ቡድን መሪ በባህርዳር ዙሪያ ወረዳ ቅንባባ ቀበሌ የሚከናወኑ የፕሮጀክቱን ስራዎች ጎብኝተዋል።