የሀገር ውስጥ ዜና

በአንዳንድ አካባቢዎች የድምጽ አሰጣጥ ተጠናቆ ድምጽ ቆጠራ ተጀምሯል

By Tibebu Kebede

June 21, 2021

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 14 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በጎንደር፣ ቻግኒ እና ደብረ ብርሃን ከተሞች 6ኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ ድምጽ መስጠት ተጠናቆ ቆጠራ ተጀምሯል፡፡

በጎንደር፣ ቻግኒ እና ደብረ ብርሃን ከተሞች የተካሄደው ምርጫ በሰላም ተጠናቆ ማምሻውን ቆጠራ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

በተመሳሳይ በሃዋሳ ፣ በወልዲያ እና ድሬዳዋ ከጠዋቱ 12 ሰዓት የተጀመረው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ተጠናቆ ድምጽ ቆጠራ ተጀምሯል፡፡

በተያያዘም ሰሜን ወሎ ዞን ባሉ ዘጠኝ የምርጫ ክልሎች ድምፅ የመስጠት ሂደት ተጠናቆ ቆጠራ ተጀመረ፡፡

የዞኑ ምርጫ ቦርድ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አይንየ ተፈራ እንደገለፁት ምርጫ በተካሄደባቸው 1 ሺህ 43 የምርጫ ጣቢያ ምንም አይነት የፀጥታ ችግር ሳይከሰት ምርጫው በሰላም ተጠናቆ ወደ ቆጠራ ተገብቷል፡፡

ጊዜያዊ የምርጫ ውጤቱም ነገ ጠዋት በየምርጫ ጣቢያዎቹ ይታወቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በይስማው አደራው፣ ስንታየሁ መሃመድ፣ አላዩ ገረመው፣ ሳምራዊት የስጋት እና በእዮናዳብ አንዱዓለም

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!