Fana: At a Speed of Life!

በደብረ ብርሃን ከተማ እና በሰሜን ሸዋ ዞን የሚገኙ የተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች ውጤት ይፋ እየሆነ ነው

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 15 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በደብረ ብርሃን ከተማ እና በሰሜን ሸዋ ዞን የሚገኙ የተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች ውጤት ተለጥፎ ዜጎችም ውጤቱን እየተመለከቱት ነው።

በተመሳይ በሰሜን ሸዋ ዞን በተዘዋወርንባቸው የምርጫ ክልሎችና የምርጫ ጣቢያዎች ውጤት እየተለጠፈ ነው።

የተለያዩ የህብረሰብ ክፍሎች ምርጫው ሰላማዊ ና ዴሞክራሲያዊ እንደነበር ገልፀው ÷ ከዚህ ቀደም ከነበሩ ምርጫዎች የተሻለ ዴሞክራሲ የሰፈነበት እንደነበር ተናግረዋል።

ምርጫ ቦርድ አጠቃላይ ውጤቱን እስኪያሳውቅ ድረስ ሁሉም በትዕግስት መጠባበቅ አለበት ያለት ደግሞ የሰሜን ሸዋ ዞን ምርጫ ቦርድ ማሰተባበሪያ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሙሉጌታ አክሊሉ ናቸው።

በአላዩ ገረመው እና በሳምራዊት የሥጋት

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.