አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ትናንት የድምጽ አሰጣጥ ሂደት ባልተጠናቀቀባቸውቦታዎ በዛሬው ዕለት ድምጽ የመስጠቱ ሂደት ቀጥሎ እየተካሄደ መሆኑን የምርጫ ቦርድ አስታውቋል፡፡
በዚህ መሰረትም በሲዳማ ክልል በሁሉም ምርጫ ክልሎች ከጠዋቱ 5 ሰአት ጀምሮ የድምጽ አሰጣጡ ሂደት የቀጠለ ሲሆን÷ በዛሬው እለትም የሚጠናቀቅ ይሆናል፡፡
በጋምቤላ ክልል ባሉ የተወሰኑ የምርጫ ክልሎች ተቋርጦ የነበረው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ዛሬ ከቀኑ 8 ሰአት ጀምሮ የሚቀጥል ሲሆን በዛሬው እለት ይጠናቀቃልም ነው የተባለው።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በሁለት ምርጫ ክልሎች ያለው ድምጽ አሰጣጥ ሂደት ለጊዜው የቆመ ሲሆን÷ ቁሳቁሶች በሙሉ ታሽገው እንዲጠበቁ ቦርዱ ለአስፈጻሚዎች አሳውቋል።
ቦርዱ የሚቀጥለው የድምፅ አሰጣጥ ሁኔታ እና እስካሁን ያለውን ሂደት ገምግሞ የደረሰበትን ውሳኔ እንደሚያሳውቀም ጠቁሟል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!