ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን አስጀምረዋል
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የአቅመ ደካሞችን ቤት በማደስ የክረምት በጎ ፈቃድ አስጀምረዋል ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ አራት ኪሎ አቧሬ አካባቢ ሰባት የአቅመ ደካሞችን ቤት ማሳደስ ጀምረዋል ።
በክረምቱ በጠቅላይ ሚኒስትሩ እና በሪፐብሊካን ጋርድ ጥበቃ አባላት እስከ 15 ቤቶች እንደሚታደሱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል ።
ሁላችንም ተባብረን በየአካባቢያችን ያሉ አቅመ ደካሞችን ህይወት ልንቀይር ይገባል ብለዋል።
በአልአዛር ታደለ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!