Fana: At a Speed of Life!

የብልጽግና ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የ6ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ሂደት ገመገመ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የብልጽግና ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የ6ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ሂደት መገምገሙን አስታወቁ፡፡

ግምገማው በቅድመ ምርጫ ዝግጅት፣ በምርጫ ክንውን፣ በሕዝብ ተሳትፎ እና በአጠቃላይ የምርጫው ሂደት ላይ ያተኮረ እንደነበር ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትዊተር ገፃቸው አስፍረዋል፡፡

ኮሚቴው ከጠቅላላ ሂደቱ ጋር በተያያዘም ደካማ እና ጠንካራ ጎኖችን መለየቱን ጠቁመዋል፡፡

ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው በሰላም እና ደኅነት እንዲሁም በቀጣይ መሠራት ባለባቸው ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ ማስቀመጡንም ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የገለጹት፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.