የሀገር ውስጥ ዜና

በአጣዬ አካባቢ የተቋቋመው የኮማንድ ፖስት የፈፀማቸውን ስራዎች ገመገመ

By Tibebu Kebede

June 24, 2021

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 17 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአጣዬና አካባቢው ተፈጥሮ የነበረውን ችግር ለመፍታት የተቋቋመው ኮማንድ ፖስት ስራ ከጀመረ አንስቶ ያከናወናቸውን ተግባራትና የተገኙ ለውጦችን በከሚሴ ከተማ ገምግሟል።

ኮማንድ ፖስቱ ለማከናወን ያቀዳቸው፣ የተፈጠረውን ግጭት የማስቆምና ወደ መደበኛ ሁኔታ የመመለስ ፣ ማህበራዊና አስተዳደራዊ ሁኔታዎችን ወደ ቀድሞ ሁኔታ የመመለስ ፣ የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ በተወሰዱ እርምጃዎችና ጥፋተኞችን ወደ ፍርድ ለማቅረብ የተገኙ ውጤቶችን አጠናክሮ እንዲቀጥል ለማስቻል እና በአፈፃፀሙ ላይ የታዩ ክፍተቶችን ለመፍታት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ነው ግምገማውን ያደረገው።

በግምገማው የዞንና የወረዳ የኮማንድ ፖስቱ አመራሮች እየተሳተፉ ሲሆን ለቀጣይ የስራ አቅጣጫ ያስቀምጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የመከላከያ ሰራዊት መረጃ ያመላክታል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!