Fana: At a Speed of Life!

የምርጫ ውጤትን ጨምሮ የምርጫ ቁሳቁስ ወደ ምርጫ ክልሎች መድረሳቸውን የሰሜን ሸዋ ዞን ምርጫ ማስተባበሪያ አስታወቀ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 18 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የምርጫ ውጤትን ጨምሮ የምርጫ ቁሳቁስ ከሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ወደ 13ቱ የምርጫ ክልሎች መድረሳቸውን የሰሜን ሸዋ ዞን ምርጫ ማስተባበሪያ አስታወቀ፡፡

የማስተባበሪያው ሃላፊ አቶ ሙሉጌታ አክሊሉ ለጣቢያችን እንዳሉት፥ ከ1 ሺህ 128ቱ ምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ውጤትን ጨምሮ ሁሉም የምርጫ ቁሳቁስ ወደ ምርጫ ክልሎች ደርሰዋል፡፡

ውጤት የመደመር ስራውም እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የምርጫ ውጤቱ በክልል ደረጃ ተደምሮ ዛሬ ይፋ እንደሚሆንም ነው የተናገሩት አስተባባሪው፡፡

የምርጫ ግብዓቶቹ ችግር ሳይደርስባቸው ወደየ ምርጫ ክልሎች እንዲደርሱ ጠንካራ ጥበቃ ያደረገውን የጸጥታ አካልም አመስግነዋል፡፡

በቀጣይም ከምርጫ ክልሎች ወደ ዞን በመሰብሰብ ለምርጫ ቦርድ ተመላሽ የሚሆን ቁሳቁስ እንዲመለሱ ይደረጋልም ነው ያሉት፡፡

ህብረተሰቡም ምርጫው ሰላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ላደረገው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበው መገናኛ ብዙሃን እውነታውን ለህዝብ ለማድረስ የነበራቸውን ትጋትም አድንቀዋል፡፡

በሳምራዊት የስጋት

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.