Fana: At a Speed of Life!

ለምርጫው ስኬታማነት ጉልህ ድርሻ ያበረከቱ አካላት የሀገር ባለውለታዎች ናቸው – አቶ እርስቱ ይርዳው

 

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 20፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ለ6ተኛው ሀገራዊ ምርጫ ስኬታማነት ጉልህ ድርሻ ያበረከቱ አካላት የሀገር ባለዉለታዎች ናቸው አሉ የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እርስቱ ይርዳው።

ክልሉ በቀጣይ የድህረ ምርጫ የልማት ተግባራትን እንዴት ያሳካ በሚል ውጥን ላይ ከከፍተኛ አመራሮች ጋር በጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ መክረዋል።

በበልጉ የዝናብ እጥረት የተከሰተውን የምርት ቅናሽ፣በመኸሩ ማካካስ የሚያስችል እቅድ ቀርቦ የተወያዩ ሲሆን የኢትዮጵያን እናልብስ ዘመቻ አካል የሆነውን የአርንጓዴ ልማት አሻራን የማኖር ስራዉ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሰፉፊ ስራዎች እንደሚሰሩም በደሬቴ የገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.