የሀገር ውስጥ ዜና

የጀነራል ሰአረ መኮንን ገዳይ በእድሜ ልክ ጽኑ እስራት ተቀጣ

By Tibebu Kebede

June 28, 2021

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የጀነራል ሰአረ መኮንን ገዳይ አስር አለቃ መሳፍንት ጥጋቡ በእድሜ ልክ ጽኑ እስራት ተቀጣ።

አቃቤ ህግ በሞት እንዲቀጣ ጥያቄ አቅርቦ የነበረ ቢሆንም 4 የቅጣት ማቅለያ በማቅረቡ ቅጣቱ በእድሜ ልክ እስራት እንዲቀል ፍርድ ቤቱ ወስኗል፡፡

የቅጣት ውሳኔው የተላለፈው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የጸረ ሽብር እና ህገ መንግስታዊ ጉዳዮች በዛሬው ዕለት በዋለው ችሎት መሆኑን ኢቢሲ ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!