Fana: At a Speed of Life!

አሜሪካ በኢራን በሚደገፉ የኢራቅ እና ሶሪያ ታጣቂ ቡድኖች ላይ የአየር ላይ ጥቃት ፈጸመች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) አሜሪካ በኢራን በሚደገፉ የኢራቅ እና የሶሪያ ታጣቂ ቡድኖች ላይ የአየር ላይ ጥቃት መፈጸሟ ተሰምቷል፡፡

የአየር ላይ ጥቃቱ ታጣቂ ቡድኖች ኢራቅ በሚገኘው የአሜሪካ ጦር ሰፈር ላይ ለፈጸሙት የድሮን ጥቃት አጸፋዊ ምላሽ መሆኑን የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

በትናንትናው ዕለት በተፈጸመው በዚህ ጥቃትም በአማጺ ቡድኖች የጦር መሳሪያ ማከማቻ መጋዝን ላይ ጉዳት ማድረስ መቻሉ ነው የተገለጸው፡፡

ከዚህ ባለፈም በጥቃቱ አምስት የሚደርሱ ታጣቂዎች የተገደሉ ሲሆን ÷ በርካቶች የመቁሰል አደጋ እንደደረሰባቸው በዘገባው ተመላክቷል፡፡

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጀ ባይድን በተለያዩ ሀገራት ሰላም ለማስከበር የተሰማሩ አሜሪካ ወታደሮችን ደህንነት ለማስጠበቅ አስፈላጊው አጸፋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ ተናግረዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ባይደን ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ የአሜሪካ ጦር በኢራቅ እና ሶሪያ ድንበር አካባቢ በሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ቡድኖች ላይ እርምጃ ሲወስድ ይህ ሁለተኛ ጊዜው ነው፡፡

ምንጭ ÷ አልጂዚራ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.