ቢዝነስ

የገቢዎች ሚኒስቴር በአስር ዓመት የብልፅግና መሪ ዕቅድ ላይ ተወያየ

By Tibebu Kebede

January 24, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 15፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የገቢዎች ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋመቱ ጋር በአስር ዓመት የብልፅግና መሪ ዕቅድ ላይ መወያየቱን አስታወቀ፡፡

የኢፌዴሪ የገቢዎች ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ዘመዴ ተረፈ÷ ሚኒስቴር ሚስሪያ ቤቱና ተጠሪ ተቋመቱ (ጉምሩክ ኮሚሽንና ብሔራዊ ሎተሪ) ሀገራዊ የብልፅግና ዕቅዱን እና የባለፉት ዓመታት የገቢ ዘርፉን አፈጻጸም መነሻ በማድረግ የ10 ዓመት መሪ ዕቅድ ማዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡