Fana: At a Speed of Life!

አየር መንገዱ በ2020 መንገደኞችን በማጓጓዝ እና በጭነት አገልግሎት ከአፍሪካ ቀዳሚነቱን ያዘ

አዲስ አበባ፣ሰኔ 25፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ በፈረንጆቹ 2020 መንገደኞችን በማጓጓዝ እና በጭነት አገልግሎት ከአፍሪካ ቀዳሚ መሆኑን የአፍሪካ አየር መንገዶች ማህበር ይፋ አድርጓል።
ማህበሩ አየር መንገዶችን በሚሰጡት አገልግሎት መሰረት አመታዊ ደረጃቸውን ይፋ ያደርጋል፡፡
መንገዱ መንገደኞችን በማጓጓዝ እና በጭነት አገልግሎት በፈረንጆቹ 2020 የአፍሪካ ቀዳሚው አየር መንገድ ተብሏል፡፡
በጭነት ከ500 ሺህ ቶን በላይ ጭነት ሲያጓጉዝ 5 ነጥብ 2 ሚሊየን መንገደኞችን ደግሞ አጓጉዟል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.