Fana: At a Speed of Life!

ግብጽ የስዊዝ ካናልን ዘግታ የቆየችውን መርከብ ለመልቀቅ ተስማማች

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 28 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) መርከቧ ላደረሰችው ጉዳት ካሳ እስከሚከፈል ድረስ እንዳትንቀሳቀስ ታግዳ ቆይታለች፡፡

ከመርከቧ ባለቤቶችና ከመድህን ኩባንያው ጋር በተደረሰው የካሳ ስምምነት መሰረት ነው ግብጽ ኤቨር ግሪን የተባለችውን መርከብ እንደምትለቅ ያስታወቀችው፡፡

መርከቧ ስዊዝ ካናልን ዘግታ በቆየችባቸው ቀናት ለደረሰው ኪሳራ ግብጽ 550 ሚሊየን ዶላር ካሳ መጠየቋን የቢቢሲ ዘገባ አመላክቷል፡፡

እስካሁን ድረስ ከስምምነት የተደረሰበት የካሳ ክፍያ መጠን ይፋ አልተደረገም፡፡

የሜዲትራንያን ባህርን ከቀይ ባህር የሚያገናኘው ስዊዝ ካናል ተዘግቶ የቆየባቸው ስድስት ቀናት በዓለም አቀፍ የንግድ ልውውጥ ላይ ከፍተኛ ጫና ፈጥሮ እንደነበር ይታወሳል፡፡

ከስዊዝ ካናል ለቃ ከወጣች በኋላም በግሬት ቢተር ሃይቅ እንድትቆይ ተደርጓል፡፡

መርከቧ ከነገ በስቲያ ረቡዕ ተለቆ ወደ መደበኛ ስራዋ ትገባለች ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.