የሀገር ውስጥ ዜና

የጌዲኦ ብሔር የዘመን መለወጫ (ዳራሮ) በዓል በድምቀት እየተከበረ ነው

By Tibebu Kebede

January 25, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 16፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የጌዲኦ ብሔር የዘመን መለወጫ (ዳራሮ) በዓል በዲላ ከተማ በድምቀት እየተከበረ ነው።

በስነ-ስርዓቱ ላይ የደቡብ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳውን ጨምሮ የተለያዩ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ አመራሮች፣ የብሔሩ አባገዳዎችና የሀገር ሽማግሌዎች ታድመዋል።