ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ258 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር የእርዳታ ስምምነት ተፈራረሙ
አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 2፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ258 ነጥብ 83 ሚሊየን ብር የእርዳታ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
የእርዳታ ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህምድ ሺዴ እና በኢትዮጵያ የጣሊያን አምባሳደር አርቱሮ ሉዚ ተፈራርመውታል፡፡
እርዳታው ለስራ ፈጠራ በተለይም አነስተኛ እና በሴቶች የሚንቀሳቀሱ የንግድ ስራዎችን ለማበረታታት ያለመ መሆኑን ከገንዘብ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!